Monday, March 25, 2013

ጊዜ ማሳለፊያ ባህሎቻችን ይቀየሩልን!


         ማልዶ መነሳት ሃላፊነት የሚሰማው ሰው መገለጫ ከሆነ አምሽቶ መግባት የግዴለሽነት መገለጫ መሆኑ ነው
ግን ግን ጊዜን ከመጠቀም አንፃር ሃያ አራት ሰዓት ሙሉ ከመስራት አኳያ ስናየው ማልዶ የወጣው ሰው
ራሱ ስራውን እስኪጨርስ ቆይቶ አምሽቶ ቢገባስነገሮችን ከአንድ አቅጣጫ ብቻ ማየታችን ዋጋ እያስከፈለን
ያለ ይመስለኛልታማኝ ባል ለመባል በጊዜ የሚገባ ባል በሌላ መንገድ ጊዜውን እየተሰረቀም ሊሆን ይችላል።
ሲጀመር ታማኝነት ከልብ የሚመነጭ ነገር ነው እንጅ ለመወስለትና ለመሴሰንማ በጠራራ ፀሀይ ካሉት ሰዓታት
ውስጥ ያሉት ጥቂት ደቂቃዎችም በቂ ናቸው። አንዳንድ የቤት እመቤቶች ግን በዚህ መንገድ ለማየት አልታደሉምና
ፊልድ የሚወጣ ባልንና ስራ አምሽቶ የሚገባ አባወራን ሁሉ በሌላኛው ግዴለሽ አባወራ ምግባር ነው የሚዳኙት።
      እስኪ እንዲህ አድርገን እንየው ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስታችን ልብም ዕውቀትም ሰጥቶት መስሪያ ቤቶች በሙሉ
እንደፋብሪካዎቹ ሃያ አራት ሰዓት መስራት ቢጀምሩ እነዚህ የጨዋ ሰዎች መስፈርቶች አፈር የሚበላቸው አይመስላቹህም?!
ሁሉም ባለትዳር ሲቪክ ሰራተኞች የለሊት ተረኛ መሆን ቢጀምሩ ቀናተኛ ሚስቶች ምን ሊውጣቸው ነው?
አያቹህ ሁሌም ከመንግስት አዲስ ነገር ሲመጣ የምንገባበት የሚጠፋን ቀድመን ስለማንዘጋጅ ነው!በዚህ ረገድ
ተረቶቻችንም ሆነ ፈሊጣዊ ንግግሮቻችን ስለኛ ከእኛ ይልቅ ያዉቁልናል "አይሆንምን ትተሽ ይሆናልን አስቢ፣
ፅድቁ ቀርቶ በወጉ በኮነንከኝ፣የባሰ አታምጣ፣ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው፣ሳታማሀኝ ብላኝ..." ይህ ሁሉ ቢሆን ግን
እኛ ሀበሾች የሐሜት በር እንጂ የጊዜ መብረር አይጨንቀንም!ተሳስተን ከመማርም ያለኝ ይበቃኛል ማለት ይቀናናል
አዲስ ህግ ወጥቶ ካልቀየረን በቀር በማህበረሰቡ ያለንን ተቀባይነት የሚያሳጣ አንድም የለውጥ እንቅስቃሴ ውስጥ
መሳተፍ አንፈልግም!
      ነገሩ ባህል ከመሰረታዊ ነገሮች በቀር በየዘመኑ የሚቀየር ቢሆንም አንዴ በተበጀ ወግና
ልማድ ተተብትበን "ባህሌን ባህሌን!" ብለን ከማቀንቀን አልቦዘንም ምክንያቱም እኛ "አይነተኛ/ቲፒካል ሀበሾች!"
ነን። ሰውን ማክበር በተለይ ለታላቆቻችን ቅድሚያ መስጠት፣እንግዳ መቀበል፣ለማተብ ማደር፣ሀገርን መውደድ፣ታሪክንና
ቅርስን መጠበቅ እና ሌሎች ባህሎቻን መሰረታዊ ስለሆኑ መቀየር አይገባቸውም ነገር ግን የዛኑ ያህል ከቴክኖሎጅ
መቆራረጥ፣ጊዜን ማባከን (ቡና በመጠጣትና ጫት በመቃም ሊሆን ይችላል)፣ራዕይንና ባለራዕይን ተስፋ ማስቆረጥ፣
የባላባት አስተሳሰብና ሌሎች ችግሮቻችንን ግን ባህል ብለን መንከባከብ አይጠበቅብንምደግሞም ይህ ትውልድ
የራሱን ባህል እንዳይገነባ ማሸማቀቅ ተገቢ አይደለም አንደኛ ዘመን ከዘመን አይበልጥም ሁለተኛ በየትኛው ዘመን
"የዛሬ ልጆች አይረቡም!" የሚል አስተሳሰብ እንደነበረ አይካድም። ሁሌም በሁለት ትውልድ መሃል ተቃርኖ
ይኖራል እያረጀ የሚመጣው ትውልድ አዲሱን ትውልድ መተቸቱ የማይቀር ነው የበጎ ባህሎቻችን ቅብብሎሽ ግን
ሁሌም ይቀጥላል ዘመኑ ይዟቸው የሚመጡ ለውጦችም ተለዋዋጭ ባህሎች ላይ ጫና እየፈጠረ መሄዱ አይቀርም።
ዋናው ነጥብ እዚህ  ነው፡ተለዋዋጭ ባህል እንደላሊበላና አክሱም ወጥ ስራዎች ተጠብቆ መኖር አለበት በሚሉ
ወግ አጥባቂዎች እጅ ሲወድቅ በመሃል ከንቱ ልማዶቻችን አብረው ሲያቆረቁዙን እንዲኖሩ እየፈረዱብን ነው።
     ዋናው ነጥብ እዚህ  ነው፡ተለዋዋጭ ባህል እንደ ላሊበላና አክሱም ወጥ ስራዎች ተጠብቀው
እንዲኖሩ በሚሟገቱ ወግ አጥባቂዎች እጅ ሲወድቅ አደጋ አለው በመሃል ከንቱ ልማዶችም ተሰግስገው እንዲያ
ቆረቁዙን እየፈረዱብን ነውና። በተለይ ጊዜ አጠቃቀማችን ከጊዜ ወደ ጊዜ በመላሸቅ ላይ ይገኛል እንዳውም
አንድ የውጭ ዜጋ የአንበሳ የከተማ አውቶብስ ቀኑን ሙሉ ተሳፋሪዎችን ይዞ በየሰፈሩ ሲሄድ አይታ "ይህ
ሁሉ ሰው በምን ሰዓት ነው ታዲያ የሚሰራው?" በማለት ትዝብቷን ገልፃለች በሌላ በኩልም መንግስት
በሃያ አራት ሰዓታት ውስጥ ስምንት የስራ ሰዓታትን ብቻ ለስራ ማወጁ ችግሩን ከድጡ ወደማጡ ዘፍቆታል
ስምንት ሰዓት ስራ፣ስምንት ሰዓት እረፍትና ምኝታ ቢሆን ስምንቱ ሰዓትስ የት ገባምናልባት ከሚያስፈልገው
በላይ እየተዝናናን ይሆናል ምናልባት ማህበራዊ ህይወታችንን እያጠነከርን ይሆናል ምናልባትም ጊዜ ተርፎን
"ጊዜ ማሳለፊያየሆሊውድ ፊልም እያየን ጫት እየቃምን ወይም ቡና ከነ "ሴረሞኒውአፍልተን
ተረኛውን ሰው እያማን ይሆናል ግን እነዚህ ባህሎች ከዘመናቸው አልፈው በዚህ ዘመን ቅቡል ሊሆኑ
ይገባ ነበርእርግጥ ነው በጊዜያቸው ስናደርጋቸው መልካም ትስስርን ይፈጥራሉ ያለጊዜያቸው ደግሞ
ሀገር አቀፍ ስንፍናን የሚፈለፍሉ ጎጂ ልማዶች ናቸው።
      እንግዲህ ጊዜን ባግባቡ ለመጠቀም ብሎም ቀንና ለሊት ለመስራት አስተሳሰባችን እስኪቀየር፣
መንግስት "እንፍራስትራክቸሩንእስኪያሳድግ ማለት መንገድና መብራት በየመንደሩ እስኪስፋፋ፣የምድሪቱ
እርግማን እስኪነሳ እንጠብቅ ይሆንከዛሬ የተሻለ ቀን ካለ ይሁና ምን ገዶን?! እስከዛው ግን "ጊዜ
ማሳለፊያ ባህሎቻችን ይቀየሩልን!" የሚል "ስሎጋንይዘን ወግ አጥባቂ ወገኖቻችንን ብንሞግታቸውስ?
ባንሞግታቸውስ?(ሳቅ)

No comments:

Post a Comment