እንዴትም አድርጎ ቢሰራህ ካፈሩ፣
አንተ ምን አገባህ ተውለት ለእግዜሩ!
ይልቅ እፍ ብሎ ከትቢያ ላነሳ፣
ምግባር ቢጎልህም ምስጋናን አትርሳ!
የምሬን ነው ጎበዝ! የ ም ሬ ን - ነ ው!
ፈጣሪን ማወደስ ምንጊዜም ለራስ ነው!
እንኳን ስጋ ለብሶ ለሞተልህ ጌታ፣
ገንዘብ ላበደረህ አለህ አንዳች ቦታ!
ደግሞ ስገስፅህ በትዝብት አትየኝ፣
ወዮልኝ ለራሴ!
እንደምክሬ ባልኖር እኔም እንዳንተ ነኝ!
ግን አየህ ወንድሜ፥
በህፃን አንደበት እንኳ ቢነገርም፣
እውነት ስለሆነ ኃይሉ አይቀየርም!
እናም አንተ ጎበዝ!
ስለምክሬ ብዛት መሰናከል ትተህ፣
ብርሃንን ልበስ ከጨለማ ወጥተህ!
እ/ር በድካም መስራቱ ካልቀረ፣
ሰው ለምን ይሞታል እንዳቀረቀረ?
የጨለማው ገዢ ጨርሶ እስኪመታ
አንተ ምን ቸገረህ ቢዘገይስ ጌታ?!
ይልቅ ና ወዳጄ!
ቅጥር እንቀጥር፥በገና እንወጥር፣
ዝማሬ ብቻ ነው ቀኑን የሚያሳጥር!
አንተ ምን አገባህ ተውለት ለእግዜሩ!
ይልቅ እፍ ብሎ ከትቢያ ላነሳ፣
ምግባር ቢጎልህም ምስጋናን አትርሳ!
የምሬን ነው ጎበዝ! የ ም ሬ ን - ነ ው!
ፈጣሪን ማወደስ ምንጊዜም ለራስ ነው!
እንኳን ስጋ ለብሶ ለሞተልህ ጌታ፣
ገንዘብ ላበደረህ አለህ አንዳች ቦታ!
ደግሞ ስገስፅህ በትዝብት አትየኝ፣
ወዮልኝ ለራሴ!
እንደምክሬ ባልኖር እኔም እንዳንተ ነኝ!
ግን አየህ ወንድሜ፥
በህፃን አንደበት እንኳ ቢነገርም፣
እውነት ስለሆነ ኃይሉ አይቀየርም!
እናም አንተ ጎበዝ!
ስለምክሬ ብዛት መሰናከል ትተህ፣
ብርሃንን ልበስ ከጨለማ ወጥተህ!
እ/ር በድካም መስራቱ ካልቀረ፣
ሰው ለምን ይሞታል እንዳቀረቀረ?
የጨለማው ገዢ ጨርሶ እስኪመታ
አንተ ምን ቸገረህ ቢዘገይስ ጌታ?!
ይልቅ ና ወዳጄ!
ቅጥር እንቀጥር፥በገና እንወጥር፣
ዝማሬ ብቻ ነው ቀኑን የሚያሳጥር!
Good job i like it ...!!!!!!!!!!
ReplyDelete